10ኛዉ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሃ ግብር

የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ቅዳሜ፣ እሁድና ሰኞ በሚደረጉ የአስረኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቀጥሎ ይዉላል።
ቅዳሜ፣ ሰባት ጨዋታዎች ሲደረጉ፣ ምሳ ሰዓት ላይ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ በማንቸስተር ዩናይትድና በቶተንሃም ሆትስፐር መካከል ኦልድ ትራፎርድ ላይ ይደረጋል። በእኩል 20 ነጥብ ላይ ሆነዉ የሚገናኙት ሁለቱ ክለቦች ማንቸስተር ከሃደርስፊልድ ሽንፈት በኋላ፣ ቶተንሃም ደግሞ ሊቨርፑልን በሰፊ ዉጤት አሸንፎ የሚያደርጉት ጨዋታ ነዉ።
11፡00 ላይ አምስት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን፣ አርሰናልና ሊቨርፑል በሜዳቸዉ፣ ማንቸስተር ሲቲ ከሜዳዉ ዉጭ ይጫወታሉ። ምሽት 1፡30 ላይ ደግሞ ቸልሲ ወደ በርንማዉዝ ሜዳ ተጉዞ የ10ኛ ሳምንት ጨዋታዉን ያደርጋል።
እሁድ ሁለት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን፣ በተከታታይ ሳምንት አሰልጣኞቻቸዉን ያሰናበቱት ሌይስተር ሲቲና ኤቨርተን ይገናኛሉ። የዚህ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ሰኞ ምሽት ይከናወናል።
ቅዳሜ፣ 28/ 2010 ዓ/ም
ማንቸስተር ዩናይትድ ከ ቶተንሃም 8፡30
አርሰናል ከ ስዋንሲ 11፡00
ክርስትያል ፓላስ ከ ዌስትሃም 11፡00
ሊቨርፑል ከ ሃደርስፊልድ 11፡00
ዋትፎርድ ከ ስቶክ ሲቲ 11፡00
ዌስትብሮም ከ ማንቸስተር ሲቲ 11፡00
በርንማዉዝ ከ ቸልሲ 1፡30
እሁድ፣ 29/ 2010 ዓ/ም
ብራይተን ከ ሳዉዛምፕተን 9፡30
ሌይስተር ከ ኤቨርተን 12፡00
ሰኞ፣ 30/ 2010 ዓ/ም
በርንሌይ ከ ኒዉካስትል 4፡00
ግርማይ መረሳ
Latest posts by ግርማይ መረሳ (see all)
- 10ኛዉ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ መርሃ ግብር - January 4, 2018
- የለንደን ደርቢ በአቻ ዉጤት ተጠናቀቀ - January 4, 2018
- ማንቸስተር ሲቲ ወደ ድል ተመለሰ - January 3, 2018
Leave a Reply